ዜና | Oduu | News
በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን ቀልጣፋና ምልልስን ያስቀረ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ሲል የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ገለፀ።

በክ/ከተማው እየተሰጠ ያለው የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት በአስተዳደሩ በየደረጃው የሚሰጡ አገልግሎቶች ፈጣን ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል በትኩረት እየሰራን ነው ብለው ከምልልስ የፀዳ አገልግሎትን ለማስፈን ተቀናጅተን እየሰራን ነው በማለት ገልፀዋል። በምንሰጠው አገልግሎት የማህበረሰቡን እርካታ በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ እየሰራን ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አገልግሎትን ማሻሻልና ማዘመን የሁሉም የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መሰረት በመሆኑ በትኩረት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ አራርሳ ድሪባ ከነዋሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጡ።

ህዝብን የሚያማርሩ እና ለመንግስት አገልግሎት ጉቦ የሚጠይቁ ካሉ እርምጃ እየወሰድን እናርማለን። በሰንበት ገብያው ላይ ደላላውን በማስወጣት አምራቹና ሸማቹ በቀጥታ እንዲገናኙ ተደርጓል። በፋብሪካና በግብርና ምርቶች አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በትኩረት እየተሰራ ነው። የአገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል እያሳየ ነው የበለጠ የማሻሻል ተግባር እየተከናወነ ነው። የቤት ፍላጎትና አቅርቦትን ለማመጣጠን በትኩረት እየተሰራ ነው። ችግሮችን መሻገር የምንችለው ህዝብና መንግስት ተባብረው ሲሰሩ በመሆኑ ተባብረን እንስራ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በራስ አቅም ተረጂነት እና ድህነትን ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የተረጂነት እና ድህነት ቅነሳ ተግባራት አፈፃፀም አጠቃላይ አመራር በተገኘበት ተገመገመ። የውይይት መድረኩን የመሩት የልደታ ክ/ከተማ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍታለው ከፍያለው ሲሆኑ የልመናና ተረጂነት ቅነሳ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ሀገራችን በተያዘው ከተረጂነት ለመላቀቅ የምታደርገውን ጥረት ማሳካት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። አስተዳደሩ በራስ አቅም ተረጂነትን ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ፍታለው የውጭ ሀገራት እርዳታ የሀገርን ክብር የሚያወርድና ተረጂነት የሚያስፋፋ በመሆኑ መንግስት በእራስ አቅም ተረጂነትን ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በየደረጃው የታዩ የአፈፃፀም ጉድለቶችን በማረም የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳይቀዛቀዙ መትጋት እንሚገባም አቶ ፍታለው ጨምረውም ገልፀዋል። የክ/ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ያየ አለም በበኩላቸው ተረጂነት የመፍጠር አቅም እና የመስራት ጉልበትን የሚያዳክም በመሆኑ በልዩ ትኩረት መስራት ይገባናል ብለዋል። በግምገማ መድረኩ ተግባሩ የደረሰበት አሁናዊ ሁኔታ ቀርቦ ውይይት የተካሄደበት ሲሆን ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ ከተማ አቀፍ የፅዳት የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ።

በጽዳት ዘመቻው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሰፋ ቶላ እንደተናገሩት ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ እየፈጠርን ከተማችን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን እየሰራን ነው ብለው በዚህም አበረታች ውጤቶችን አስመዝግበናል በማለት ገልፀዋል። አቶ አሰፋ አክለውም መንግስት የግንዛቤ ስራውን በማጠናከር ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ እንዲፈጠር ከማድረግ ባለፈ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትም እንዲሻሻል ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ሲሉ ገልፀዋል። ስማርት ሲቲን ለመገንባት የተያዘው ስራ እንዲሳካ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓታችንን የማዘመን ስራ እየተሰራ መሆኑንም አቶ አሰፋ ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ እንደተናገሩት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ፅዱ ውብና ለኑሮ ተስማሚ የሆነች ከተማን ለመፍጠር በትኩረት ተሰርቷል ብለው በዚህም ስኬታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። አቶ ገዛኸኝ አክለውም ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠር የቤት ለቤት ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራም ጭምር ሲሰራ ነበረ ብለው በዚህም ውብ ፅዱና ለኑሮ ተስማሚ ከተማን እየፈጠርን ነው በማለት ተናግረዋል። ማህበረሰቡ ውብና ፅዱ ከተማ ለመፍጠር ፅዳትን ከግቢው መጀመር አለበት ያሉት አቶ ገዛኸኝ ማህበረሰቡ ከፅዳት ባለፈ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓቱንም እንዲያሻሽል ጥሪ አቅርበዋል። የልደታ ክ/ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ ዓለም እንደተናገሩት ንፁህ አካባቢን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራን ነው ብለው በዚህም ቆሻሻን የሚፀየፍ ትውልድ እየገነባን ነው በማለት ገልፀዋል። ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለመፍጠር በትምህርት ተቋማትም የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ያየህ ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና የመልካም አስተዳደርና ቅሬታ አፈታትን አፈፃፀም ገመገመ።

የልደታ የልደታ ክፍለ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ቤት የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸምን ከወረዳ አመራሮች ቡድን መሪዋችና ባለሞያዋች ጋር ገምግሟል። በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት በቅንጅት የተሰሩና ጥሩ ውጤት የተመዘገበባቸው ናቸው ብለው ይህ ተግባር እንዲሳካም ሲሰሩ ለነበሩ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል። የክ/ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ ዓለም በክፍለ ከተማዉ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት እየተሰሩ ያሉ ስራዋች አበረታችና ችግር ፈቺ መሆናቸዉን ገልፀዉ በቀጣይ ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉ ገልፀዋል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ መቅደስ ያደታ በበኩላቸው የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የተሻ እንደተፈፀመና በቀጣይ ግን አገልግሎት አሰጣጡን ለማለቅ እንዲቻል ተከታታይነት ያለዉ ስራ መሰራት እንዳለበት አስቀምጠዋል :: የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሩብ ዓመቱ ስኬታማ ስራ ተሰርቷል ያሉ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ "ሳምንታዊ "የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።

በዘመቻው የክ/ከተማው አፈ ጉባኤ አቶ ዘሪሁን ሺፈርዳ /የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ጢቂ ድሪባ ፣የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ተወካይ አቶ እንግዳው ጋዴ፣አርቲስቶች ፣የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈውበታል። የልደታ ክ/ከተማ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዘሪሁን ሺፈርዳ በዘመቻው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ፅዳት የአንድ ተቋም ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ህብረተሰብ ቅንጅታዊ ተግባር ነው ብለው ማህበረሰቡ ፅዳትን ባህሉ በማድረግ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ አዲስ አበባን መፍጠር ይኖርበታል ብለዋል። አቶ ዘሪሁን አክለውም ብሎክ ሲፀዳ በድምር ውጤት ወረዳ ይፀዳል፤ ወረዳ ሲፀዳ ክ/ከተማ ሁሉም ክ/ከተሞች ሲፀዱ ደግሞ ከተማችን ውብ ትሆናለች ብለዋል። የክ/ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ ዓለም በበኩላቸው ሁላችንም ለአካባቢ ፅዳት ትኩረት በመስጠት ከተማችንን ውብና ማራኪ ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል። አካባቢያችንን ዘወትር በማፅዳት ውብ፣ ፅዱና ምቹ የሆነ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር ይኖርብናል ብለዋል። አቶ ያየህ አክለውም አዲስ አበባን እንደ ስሟ ንፁህና ፅዱ እናደርጋለን ለዚህም ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት፥ ህብረተሰቡ ዘውትር አከባቢውን ማፅዳትና ቆሻሻን በተገቢው ቦታ ማከማቸት እንደሚኖርበት ተናግረዋል #ፅዳት የዘመናዊነት መገለጫ ነው!! #ዘውትር አከባቢያችን በማፅዳት ፅዱ፣ ውብና ለመኖሪያ ምቹ የሆነ ስፍራን እንፍጠር!!

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ቆሻሻን በተገቢው መንገድ በማስወገድ ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እንዲፈጠር እየሰራ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ገለጸ።

ጽ/ቤቱ ከተማ አቀፍ በማሆበረሰቡ የደረቅ ቆሻሻ ከምንጩ የመለየት ንቅናቄ ማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ የጽዳት አምባሳደሮች፣ባለሙያዎች፣የሽርክና ማህበራት፣ ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየ ዓለም እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝን በማስተካከልና ከምንጩ በመለየት በቅብብሎሽ በማጓጓዝ የሚፈለገው ቦታ በማድረስ አካባቢያችንን በንጽህና በመያዝ ለመኖሪያ ምቹ እንድትሆን በመተባበር ልንሰራ የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት አዲስ አበባ ከተማን ገጽታ የቀየሩ በርካታ የልማት ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸው ቆሻሻን በየቦታው ከመጣል ተቆጥበን ቆሻሻን በአግባቡ በመለየትና መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል አካባቢያችን ለመኖሪያ ምቹ የተጀመሩ የልማት ስራዎችም ቀጣይ እንዲሆኑ መስራት የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፍ አሰራርን በመተገበርና አገልግሎቱን በማዘመን ውጤታማ ስራዎች መሰራቱ ተገለፀ ፡፡

የልደታ የልደታ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ማዘጋጃ ቤታዊ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ። ጽ/ቤት በተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ የ1ኛ ሩብ ዓመት ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል። የልደታ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደረጄ ተሪቦ እንደገለፁት በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ላይ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን በማከናወን በርካታ የማህበረሰብ ክፍል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል ። የከተማውን የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን በማዘመንና በጥራት በመስጠት የተገኘውን ውጤት ማስቀጠል ይገባል ያሉት አቶ ደረጄ አያይዘው ቀጣይም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማከናወን እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል። በወቅቱ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቱ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቶ ደረጄ ተሪቦ ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ያየ ዓለም በክፍለ ከተማው የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተቀላጠፈ ውጤታማና ዘመናዊ አሰራር በመዘርጋት የከተማውን የክ/ከተማውን ዕድገት በሚመጥን መንገድ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀዋል። ስራዎችን በቅንጅትና በቁርጠኝተነት በተዋረድ በመስራት እየመጣ ያለውን ውጤት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል። በክፍለ ከተማው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን በተቀላጠፈ አሰራር ዘርፈ ብዙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመቅረፍን የገለፁት አቶ ያያ አያይዘው በተቀናጀ አግባብ ተግባራትን መፈፀም እንደሚገባ ገልፀዋል። የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዘመድኩን በቀለ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈና በተቀናጀ ተግባራት በመፈፀም የተሻለ ውጤት እየመጣ እንደሆነ ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም በፅዳት ዙሪያ ከተማውን ውብና ፅዱ ከማድረግ አንፃር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አጠናክረን መስራት ይገባል ብለዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ የፅዳት ዘመቻ ተከናወነ።

የፅዳት ዘመቻውን የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤትና ከወጣት ማህበር ጋር በመተባበር ነው ያካሄዱት። የዘመቻው ዓላማ ውብ ፅዱና አረንጓዴ አካባቢን በመፍጠር ሂደት ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን ተገልጿል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ሙስናን እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቅንጅት መታገል እንደሚገባ ተገለፀ።

ስልጠናውን የክፍለ ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ከክ/ከተማ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና መከታተያ ክፍል ጋር በመተባበር ተሰጥቷል በመድረኩ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የጽዳት አምባሳደር ታዋቂ አርቲስቶች እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተገኝተዋል ተካፍለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ያየህ አለም እንዳሉት የሥነ ምግባር ጉድለትና ሙስናና ብልሹ አሰራር የሚፀየፍና የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ ለመፍጠር በሚደረገው የፀረ ሙስና ትግል ላይ የራሱን ሀላፊነት በመወጣት እንዳለበት ገልፀዋል የስልጠና ተሳታፊዎችም ስልጠናው የተሻለ መሆኑን በመግለፅ በሚደረገው የፀረ ሙስና ትግል ላይ ሁሉም የራሱን ሀላፊነት መወጣት አለበት በማለት አንስተዋል።

image
image
image
image